በድምቀት ተከበረ።
የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ጽ/ቤት በዓለም 115ኛውን በሃገራችን ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (March
“የሴቶች ድምጽ ለእኩልነትና ለበለጸገች ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል።
የእንኳን ደህና መጣችሁና አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ተወካይ ዶ/ር ሃፍታይ ገ/የሱስ ሴቶች በውሳኔ ሰጪነት ቦታዎች ላይ ያላቸውን ተሳትፎ ከዚህ በላይ ለማሳደግና ለማብቃት እንደ ዩኒቨርስቲ እየተሰራ እንደሚገኝም ገልፀው ሴቶች በውሳኔ ሰጭነትም ሆነ በተሰማሩባቸው ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ የስራ ዘርፎች ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል።
Read more: በዩኒቨርሲቲው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (March”የኢትዮጵያ ሴቶች የ50 ዓመታት የለውጥ ጉዞና የማርች 8 ታሪካዊ ፋይዳ” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ጽሁፍ በወ/ሮ ይርጋለም ነጋሽ አማካኝነት ለተሳታፊዎች ቀርቦ የፓናል ውይይት ተካሂዷል።
በዩኒቨርሲቲው የስነዜጋና ስነምግባር ትምህርት ክፍል መምህርት በሆኑት መ/ር መብርሂት ተስፋይ “ሴት የዩኒቨርሲቲ መምህራን አስተማሪ ብቻ ሳይሆኑ መጭውን ትውልድ በመቅረጽ ጉልህ ሚና የሚጫወቱ መሪዎች፣ መካሪዎች እና አርአያ ናቸው” በሚል ርዕስ የፓናል መወያያ ጽሁፍ ቀርቦ ሴት ምሁራን ያሉበትን ነባራዊ ሁኔታ፣ ለሀገር እድገት ያላቸው አስተዋጽኦ፣ የሚያጋጥሟቸው ፈተናዎችና ተተኪ ሴት ምሁራንን ለማፍራት ያላቸው ሚና ላይ በስፋት ተወያይተዋል።
የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ጽ/ቤት ሓላፊ ወ/ሮ ይርጋለም ነጋሽ በመድረኩ እንደተናገሩት
ሴት ወደቤት የሚለው አባባል በብዙ ፈተናዎችም ቢሆን ተሰብሮ ሴት ትችላለች የሚለውን መርህ በማንገብ ሴት ሃገርን ከምታሻግር ደረጃ ላይ መድረስም ተችሏል ብለዋል።
በዕለቱም በዓሉን የሚያደምቁና የሚዘክሩ በዩኒቨርስቲው የሙዚቃና ኪነ-ጥበብ ቡድን የተዘጋጁ ሙዚቃና የስነጥበብ ስራዎች ቀርበዋል።
በፕሮግራሙ ላይ የዩኒቨርሲቲውና ከተማ አስተዳደሩ ሴት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ ሰራተኞች፣ ሙህራንና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ እንግዶችም ተገኝተዋል።