Providing quality teaching and learning programs across undergraduate and postgraduate levels, fostering knowledge, skills, and critical thinking in students.

Conducting research that addresses local and national challenges, and engaging with the community through outreach, training, and development projects.

Managing the university’s operations, policies, and resources efficiently to support academic programs, staff, and students.

AdU Service

ICT Services

The ICT Directorate at Adigrat University provides essential technology services that support the university’s teaching, learning, research, and administrative activities.

AdU Data Center

Management and maintenance of the university’s servers, storage systems, and IT infrastructure to ensure reliable access to data and applications.

AdU CCTV Service:

Installation and management of security cameras and surveillance systems to ensure campus safety and monitor university facilities.

VDI Services (Virtual Desktop Infrastructure):

Provision of virtual desktops for students and staff, enabling access to university applications and resources from anywhere.

Support for Digital Learning and Online Exams:

Technical support for e-learning platforms, digital libraries, and online examinations (CBT), ensuring smooth and secure digital learning experiences.

Adigrat University (AdU)

Latest Events

Stay updated with the latest news, events, and activities at Adigrat University (AdU).

በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ ለ3ኛ ዙር ተጠናክሮ ቀጥሏል

የተፈጥሮ አካባቢን ለመጠበቅ፣ የዩኒቨርሲቲውን የአረንጓዴ አሻራ ግብ እውን ለማድረግ እንዲሁም በ3ኛ ዙር የምግብ ዋስትናን ለማጠናከር ያለመው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች፣ መምህራን፣ የአስተዳደር ሠራተኞችና ተማሪዎች በሚያደርጉት ንቁ ተሳትፎ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በዛሬው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ገ/ምክኤል ወ/ገብርኤል፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ መምህራንና የአስተዳደር ሠራተኞች ንቁ ተሳትፎ አድርገዋል።

በመርሃ ግብሩ የፍራፍሬ ልማትን ለማስፋፋትና ለምግብ ዋስትና አስተዋጽኦ ለማበርከት ዓላማ ያደረጉ የማንጎ አፕል፣አፕል፣ አበካዶ፣ ግሪፕ ተተክለዋል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ገ/ምክኤል ወ/ገብርኤል በመርሃ ግብሩ መጠናቀቂያ ላይ እንደገለጹት፣ የአረንጓዴ አሻራ ልማት የአንድ ወቅት ዘመቻ ሳይሆን አካባቢን ከጥፋት በመጠበቅ ለኑሮ ምቹ የሆነ አካባቢ ለመፍጠር የሚያስችል ዘላቂ አገራዊ ጥረት ነው። በመሆኑም መላው የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ የተተከሉ ችግኞችን በአግባቡ በመንከባከብ የመትረፍ ሁኔታቸውን ማረጋገጥ እንዳለበት አሳስበዋል።

በመርሃ ግብሩ መጨረሻም በ2017 ዓ.ም. ክረምት የተተከሉ ችግኞች የአካል ምልከታ ተካሂዷል። ምልከታው በቀደሙት ዓመታት የተተከሉ ችግኞች ያሉበትን የእድገትና የጤና ሁኔታ ለመገምገምና ተገቢውን እንክብካቤ ለማድረግ ያለውን ሁኔታ ለመለየት ተካሂዷል።

የግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ንጉሰ ገብሩ(ተ/ፕሮፌሰር) በበኩላቸው፣ የሚተከሉት ችግኞች ዋና ዓላማ የዩኒቨርሲቲውን መልክዓ ምድር ማስዋብና አረንጓዴ ሽፋኑን ማሳደግ መሆኑን ገልጸዋል። ሁሉም የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ በዚህ ተግባር ላይ የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ በማቅረብ፣ ኮሌጁም ከጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር የተተከሉ ችግኞች በአግባቡ እንዲንከባከቡና እንዲጸድቁ በቁርጠኝነት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በቀጣይም የአረንጓዴ አሻራ ልማቱን በማስቀጠል፣ ችግኞችን በአግባቡ በመንከባከብ፣ የአካባቢ ጥበቃን በማጠናከርና የፍራፍሬ ልማትን በማስፋፋት አረንጓዴና ለኑሮ ምቹ የዩኒቨርሲቲ ግቢን ለመፍጠር እንዲሁም ለምግብ ዋስትና የሚኖረውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ በቁርጠኝነት ይሠራል።

Adigrat University Receives Support to Strengthen Physics Laboratories

Adigrat University has received laboratory equipment to strengthen teaching, learning, and research activities in the Department of Physics under the College of Natural and Computational Sciences.

The handover ceremony was attended by senior university officials, college leadership, faculty members from the Department of Physics, and other members of the university community.

The initiative originated from the continued professional engagement of Professor Baker Farangis, who served the Department of Physics at Adigrat University with dedication in teaching and laboratory activities. Following the conflict in the area, Professor Baker left Adigrat University and moved to Germany, where he is currently working at Technische Hochschule Mittelhessen – University of Applied Sciences.

Professor Baker has previously contributed to strengthening academic and professional linkages between Adigrat University and German universities by facilitating institutional collaborations and partnerships.

Through his continued professional relationship with Mr. Gebregiorgis Haileslassie, a lecturer and researcher in the Department of Physics, efforts were made to identify potential sponsors who could support the rehabilitation and strengthening of the University’s Physics laboratories, which were affected by the conflict.

As a result of these efforts, Dr. Meenaxi Barkataki Ruscheweyh provided financial support, covering the full cost of laboratory equipment required by the Department of Physics, in the name of her late husband Professor Dr. Stephan Ruscheweyh.

The donated equipment includes Solar Energy and laboratory materials and instruments for Mechanics and Heat, Waves and Optics, Electricity and Magnetism, Wood Workshop, as well as other areas of physics education and practical training.

Speaking on the occasion, Mr. Mahari Gebresadik, Head of the Department of Physics, stated that the department had officially received a range of laboratory equipment. He noted that the materials will play a significant role in strengthening practical education, enhancing students’ experimental skills, and improving laboratory services.

Dr. Haftay Gebreyesus, Representative of the Vice President for Academic and Research Affairs, expressed appreciation to Mr. Gebregiorgis Haileslassie for his efforts in facilitating the support. He emphasized that the collaboration represents a valuable achievement for the University.

According to Dr. Haftay, such collaborations not only contribute to strengthening the teaching and research capacity of the Department of Physics but can also inspire other academic departments to establish similar partnerships with international institutions and professionals.

Overall, the support is expected to make a significant contribution to strengthening practical physics education, enhancing students’ experimental and research capacities, and further advancing Adigrat University’s international academic partnerships and collaborations.

የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅና ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ2019 ዓ.ም. ዓመታዊ የሥራ ዕቅድ አጸደቁ

የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅና ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ2019 ዓ.ም. ዓመታዊ የሥራ ዕቅድ በኮሌጁና በሆስፒታሉ አመራሮች፣ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በተሳተፉበት የምክክር መድረክ አጸደቁ።

መድረኩን በይፋ የከፈቱት የኮሌጁና ሆስፒታሉ ሓላፊ በመወከል ዶ/ር አባዲ ኪ/ማርያም የ2019 ዓ.ም. ዕቅዱ የ2018 ዓ.ም. የሥራ አፈጻጸም ላይ በተደረገ ግምገማ በተገኙ ልምዶች፣ ጥንካሬዎችና ተግዳሮቶች ላይ ተመሥርቶ መዘጋጀቱን ገልጸዋል።

ዕቅዱ የሰው ኃይል አቅምን ማጎልበት፣ የሠራተኞችን ተነሳሽነትና ተጠያቂነት ማሳደግ፣ የሆስፒታሉን አሠራር ዲጂታላይዝ ማድረግ፣ የጤና መረጃ ሥርዓትን ማጠናከር፣ የፋይናንስ ሀብትን በብቃት መጠቀም፣ የገቢ አቅምን ማሳደግ እና የጤና አገልግሎትና መሠረተ ልማት አቅምን ማስፋትን ያካትታል፣ ዘመናዊ መሳሪያዎች ማሟላት፣ የተገልጋይ እርካታ ከፍ ማድረግ ይገኙበታል።

በቀረበው ዕቅድ ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዶ ጥያቄዎች፣ አስተያየቶችና የማሻሻያ ሐሳቦች ቀርበዋል። የሆስፒታሉ ቺፍ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ጋይም ገ/ስላሴ፣ የአካዳሚክና ምርምር ዳይሬክተር ዶ/ር ጣሰው አብርሃ እና ማኔጂንግ ዳይሬክተሩ አቶ ገ/መድህን ሓጎስ ለተነሱት ጉዳዮች ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል።

በመጨረሻም የ2019 ዓ.ም. የሥራ ዕቅዱ በትብብር፣ በተጠያቂነትና በተቀናጀ አመራር በተግባር እንዲተረጎም አፅንዖት ተሰጥቷል። ዕቅዱም የተሻለ የጤና አገልግሎትና የተሻለ የሆስፒታል አፈጻጸም ለማስመዝገብ ያለመ ነው።