Providing quality teaching and learning programs across undergraduate and postgraduate levels, fostering knowledge, skills, and critical thinking in students.

Conducting research that addresses local and national challenges, and engaging with the community through outreach, training, and development projects.

Managing the university’s operations, policies, and resources efficiently to support academic programs, staff, and students.

AdU Service

ICT Services

The ICT Directorate at Adigrat University provides essential technology services that support the university’s teaching, learning, research, and administrative activities.

AdU Data Center

Management and maintenance of the university’s servers, storage systems, and IT infrastructure to ensure reliable access to data and applications.

AdU CCTV Service:

Installation and management of security cameras and surveillance systems to ensure campus safety and monitor university facilities.

VDI Services (Virtual Desktop Infrastructure):

Provision of virtual desktops for students and staff, enabling access to university applications and resources from anywhere.

Support for Digital Learning and Online Exams:

Technical support for e-learning platforms, digital libraries, and online examinations (CBT), ensuring smooth and secure digital learning experiences.

Adigrat University (AdU)

Latest Events

Stay updated with the latest news, events, and activities at Adigrat University (AdU).

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትና የ2019 ዓ.ም ዓመታዊ ዕቅድን ገመገመ

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትና የ2019 ዓ.ም የበጀት ዓመት የተቋማዊ ዕቅድን በተመለከተ ከዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላትና ከከፍተኛ አመራሮች ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል። መድረኩ የባለፈውን ዓመት የሥራ አፈጻጸም ለመገምገምና የመጪውን ዓመት ተቋማዊ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች በተቀናጀ መልኩ ለመተግበር ያለመ ነው።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ገብረሚካኤል ወልደገብርኤል በመክፈቻ ንግግራቸው፣ ያለፈውን ዓመት የሥራ አፈጻጸም መገምገምና ለአዲሱ የበጀት ዓመት ዕቅድ ማውጣት የዩኒቨርሲቲውን ስትራቴጂያዊ ግቦች ለማሳካት ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። የተቋሙን ጥንካሬዎች በማስጠበቅ፣ ያሉ ክፍተቶችን በማረም፣ ግልጽ ዕቅድና ተጠያቂነት በማስፈን እንዲሁም ያሉ ሀብቶችን በብቃት በመጠቀም በትብብር መሥራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።

የ2018 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትና የ2019 ዓ.ም ዓመታዊ ዕቅድ የቀረቡት በስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ አቶ ባህታ አለነ ነው። ተሳታፊዎችም በቀረበው ሪፖርትና ዕቅድ ላይ ጥያቄዎች፣ አስተያየቶችና ምክረ ሐሳቦችን በማቅረብ ሰፊ ውይይት አካሂደዋል።

የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራር በተሳታፊዎች ለተነሱት ጉዳዮች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥቷል። በመጨረሻም የ2019 ዓ.ም ዓመታዊ ዕቅድ ከተሳታፊዎች በቀረቡ ግብዓቶች እንዲጠናከርና በተሳካ ሁኔታ ወደ ትግበራ እንዲገባ የጋራ መግባባት ተደርሷል።

በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን የ2ኛ ዙር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተከናወነ

ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን የበለጠ አረንጓዴና ውብ ለማድረግ ከታቀዱ የክረምት ወቅት መርሃ ግብሮች መካከል አንዱ የሆነው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ዛሬ ነሓሴ 07/2018 ዓ.ም. ለ2ኛ ዙር በዩኒቨርሲቲው ተከናውኗል።

በመርሃ ግብሩ የዩኒቨርሲቲው ፕረዚዳንት ዶ/ር ገ/ምክኤል ወ/ገብርኤል ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች፣ የዩኒቨርስቲው ካውስል አባላት ተሳትፈዋል።

የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ በተቀናጀና በተደራጀ መልኩ በመቀጠል የዩኒቨርሲቲውን ገጽታ በሚያሻሽልና የበለጠ አረንጓዴ በሚያደርግ ሁኔታ እስከ ነሓሴ 15/2018 ዓ.ም. ድረስ የሚቀጥል ይሆናል።

የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ አመራሮች በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘውን የሠራተኞች የሕፃናት ማቆያ (Daycare) ማዕከል ጎበኙ

የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ አመራሮች ለመምህራንና ለድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች የሕፃናት ማቆያ (Daycare) አገልግሎት ለመስጠት በዩኒቨርሲቲው ግቢ እየተገነባ ያለውን ማዕከል ጎበኙ።

በጉብኝቱ የዩኒቨርሲቲው ም/ፕሬዚዳንቶች ዶ/ር ገብረኪዳን ተስፋይ እና ፅጋብ አረጋዊ (ተባባሪ ፕሮፌሰር) እንዲሁም ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የሕፃናት ማቆያ ማዕከሉ ለብዙ የዩኒቨርሲቲው ሠራተኞች የነበረ ጥያቄ በመሆኑ፣ ማዕከሉ በመጠናቀቅ ላይ ያለበትን ደረጃ በማየታቸው አመራሮቹ ደስታቸውን ገልጸዋል።

የዩኒቨርሲቲው የሥርዓተ ፆታና አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ይርጋለም ነጋሽ እንደገለጹት፣ የሕፃናት ማቆያ ማዕከሉ በመጠናቀቅ ላይ ሲሆን፣ በቅርቡ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ በመጪው አዲስ ዓመት ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆን ገልጸዋል።

ማዕከሉ በመምህራንና በድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች የሥራና የቤተሰብ ሃላፊነትን ለማመጣጠን እንዲሁም ለሠራተኞች ምቹ የሥራ አካባቢ ለመፍጠር የሚያግዝ አገልግሎት ይሰጣል።